ኢትዮጵያ የወጣቶች ሀገር ናት በታሪኳ ተከብራ የኖረችው በወጣቶች ግንባር ቀደም መሪነት እና ተሳትፎ ነው.የኢትዮጵያ ወጣቶች ለውጡን ለመፍጠር ከፍተኛ መስዋዕትነት ከፍለናል በለውጡ ሂደት በተመዘገቡ ድሎች ውስጥ የማይተካ ሚና ተጫውተናል. በለውጡ ዘመን ሊጋችን በየደረጃውና በየዘርፉ በተለይም በበጎ ፍቃድ ስራ ጀምሮ ጠቅላይ ሚኒስትራችን ያመነጯቸውን በርካታ የብልፅግና ሀሳቦች ተግባራዊ ለማድረግ እጅግ አመርቂ ርብርብ አድርገናል እንደ ክፍለ ከተማችንም በርካታ ተግባራትን በስኬት አጠናቀናል. ውድ የክፍለ ከተማችን ወጣቶች ኢትዮጵያ ደምቃ የምናያት ግን በምኞት ሊሆን አይችልም በወጣቶች የምትሰራ የተሻለች ኢትዮጵያን ነገ ለማየት ዛሬ አንድ ሆነን መቆም አለብን። አንድ ሆነን መቆም የምንችለው በሊጋችን ግንባር ቀደም ትግልና መሪነት ህብረታችንን የሚሸርብሩ ፅንፈኝነት፣ዘረኝነት፣ሌብነትን የመሰሉ ተሻጋሪ ህመሞችን ዛሬውኑ መታከምና መዳን ስንችል ነው።ለዚህ ወሳኝ ትግል እንትጋ።

የብልፅግና ፓርቲ ወጣቶች ሊግ ዓላማዎች

 የብልጽግና ፓርቲ ፕሮግራም በወጣቱ ውስጥ ሰርፆና ተግባራዊ ሆኖ መላው የአገራችንን ወጣቶች ተጠቃሚነታቸውን ማረጋገጥ፡፡
 ወጣቶች በዲሞክራሲ ስርአት ግንባታ ሙሉ በሙለ ተሳታፉ እንዲሆኑ በማድረግ በየደረጃው ባለ የልማት የዳሞክራሲና የሰላም ግንባታ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ማስቻል፡፡
 ወጣቶች ህገ-መንግስቱ ያጎናፀፋቸውን ሰብአዊና ዳሞክራሲያዊ መብቶች በትክክል ስራ ላይ እንዱውል ጠንካራ አደረጃጀት በመፍጠር ለመብታቸው እንዲታገሉ ማስቻል፡፡
 የብልፅግና ፓርቲ ወጣቶች ሊግ የወጣቶችን አቅም በመገንባትና የወጣቶች እኩልነት የሚገድቡ ባህሊዊና ልማዲዊ ተጽዕኖዎችን በመለየት በሀገር ዕድገት እና በወጣቶች ላይ የሚፈጠሩትን ተጽዕኖ በማስገንዘብ እንዱወገዱ በማድረግ ወጣቶች በውሳኔ ሰጪነት እኩል እንዱሳተፉ ማድረግ፤
 ወጣቶች የፈጠራ ዝንባሌያቸው እንዱጎለብት፣ የቴክኖልጂ ተጠቃሚ እንዱሆኑ እና የስራ ባህላቸው ዳብሮ ስራ ፈጣሪ በመሆን እራሳቸውን እና ሀገራቸውን ከድህነት በማውጣት የሚታገለ እንዲሆኑ ማድረግ፤
 ወጣቶች ህብረ ብሄራዊ አንድነታቸውን በመጠበቅ የመተሳሰብና የመረዳዳት ባህል በማጎልበት በሀገራዊ ጉዳዮች ገንቢ ሚና እንዲጫወቱ ማስቻል

የብልጽግና ወጣቶች ሊግ መርሆዎች

 ህዝባዊነት
 ዳሞክራሲያዊነት
 የህግ የበላይነት
 ልማትና ፍትሃዊ ተጠቃሚነት
 ተግባራዊ እውነታ
 ሀገራዊ አንድነትና ህብረ-ብሄራዊነት

የብልጽግና ወጣቶች ሊግ እሴቶች

 ህብረ-ብሄራዊ አንድነት
 ወንድማማችነት/ እህትማማችነት
 የዜጎች ክብር እና እኩልነት
 ነጻነት
 መከባበር እና መቻቻል
 እኩል ተሳትፎ እና ፍትሀዊ ተጠቃሚነት