በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ “በጎነት ለማህበረሰብ ለውጥ” በሚል መሪ ቃል አየተከናወነ የሚገኘው የ2017 ዓ.ም የገና በዓልን ምክንያት በማድረግ በሎው ኮስት ለሚገኙ የዝቅተኛ የማበረሰብ ክፍሎች ማዕድ ማጋራት መርሀ ግብር አካሄደ።

በእለቱ በስፍራው በመገኘት የማዕድ ማጋራት መርሀ ግብሩን ያስጀመሩት የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አድማሱ ደቻሳ እንዳሉት በዓሉ የአንድነት የፍቅር የመተሳሰብ የአብሮነት እንዲሆን እየተመኘው ያላችሁን ማንኛውንም ጥያቄዎች የክፍለ ከተማ አስተዳደሩ ደረጃ በደረጃ ፈጣን ምላሽ እንደሚሠጥም ገልፀዋል።

የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ የብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ፈንታሁን ሌማንቾ አክለው በዓሉን በእህታማማችነትና ወንድማማችነት መንፈስ ያለንን እየተጓደስ በጋራ እየተባበርን በአንድነት በዓሉ እናክብር ሲሉ መልካም የገና በዓልም እንዲሁም ምኞታቸውን ገልፀዋል።

የለሚ ኩራ ኮሚኒኬሽን
ታህሳስ 28/2017 ዓ.ም

Tags: No tags

Add a Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *